አክሱም…የብቃት ስም! ሙሉጌታ ተስፋዬ
አክሱም…የብቃት
ስም! ሙሉጌታ ተስፋዬ
የህያዋን
ልሣን …
የሰማዕታት
ድርሳን…
አኩሱም
… የብቃት ስም!
ያረጋውያን
ምክር …
የነዳያን
ዝክር …
የንፉግ
ክርክር …
የጎጆ
ፉክክር …
ማተብ
ባንገት ሲውል ታሠረ ባንድ ክር!
በሦስትዮሽ
ህብር …
በደሙ
እንዲከብር …
ባመነበት
ሊያብር …
ለሕይወት
ሊገብር …
ህብር
…
የህያዋን
ልሳን
የሰማዕታት
ድርሣን …
አኩሱም
… የብቃት ስም …
ዕምነትና
ዕውነት …
ሰውና
ሰውነት …
አኩሱም
… የብቃት ስም …
አንዱ
ላንዱ ቆሞ …
አንዱ
ላንዱ ሞቶ …
ፍቅር
ተሸምቶ … ብይን ተገምቶ …
አልሰሜንም
አምቶ …
ብሎም
ለራስ ጉዳይ … ብሎም ላንጀት ግዳይ …
ባይዘሩትም
ይበቅላል እንደበልግ እንጉዳይ …
አኩሱም
የጧት ፀሓይ …
የብርሃን
ለሐይ …
የግንባር
ምስክር …
የዕምነት
የፅናት ክር …
የህያዋን
ልሣን
የስማዕታት
ድርሣን
አኩሱም
… የንጋት ስም …
ባይን
አይቶ ለይቶ …
እህ ብሎ
ሰምቶ …
እንደሰም
ተስማምቶ …
ስውር
የከሰት … ህቡዕ የገለጠ
ካስብ
ፍጥነት በላይ … ቀድሞ ያሰለጠ …
በነፍስ
የታደመ … ከንውር ያመለጠ …
ዕምነትና
ዕውነት
ሰውና
ሰውነት …
አኩሱም
… የፅናት ስም …
‘ርጉምን
ታግሶ …
ንፉግን
ደግሶ …
አፈናን
አንግሶ …
በሦስትዮሽ
ህብር …
በደሙ
ሊከብር
ባመነበት
ሊያብር
ለሕይወት
ሊገብር …
አኩሱም
… የህብር ስም …
ስርየትን
ከፅርፃት …
ፍቅርን
ከይቅርታ …
ንቃትን
ከእምርታ …
በህያዋን
ህዋ … በሰማዕታት ተርታ …
እኩል
ተሰልፎ …
ፈተናውን
አልፎ …
እንደሰንደቅ
ቆመ
ብቃቱን
ጠቆመ!
ዝማሬውን
ካዕዋፍ …
ቅኔውን
ከቀን ጧፍ…
ማህሌቱን
ከአፀድ …
ገድ አለን
ግዴታ …
የህያው
ውዴታ …
ከተፈጥሮ
ታርቆ …
አሻግሮ
ሲያማትር … ሲመረምር ጠልቆ …
ሲያስተውል
አርቆ
ትንቢቱ
ንግሩ …
የዕድሜ
ሽግግሩ …
በጊዜው
ለሚዜው …
አንደበቱን
ከፍቶ … ቃል አመሳጠረ …
ሰማዕት
በቀለ … አኩሱም ሰው ፈጠረ …
እንደወርቅ
በሳት … በጋመው ነጠረ …
ደሞ አነጣጠረ
…
አለ አኩሱም
…
በኛው
ከኛው ለኛው …
በኛው
ስም … በኛው ስም …
ምድር
ጦም አይደር …
አገር
አይበደር …
ወራቱ
መብራቱ …
እራቱ
ኩራቱ …
ሠላሙ
ፍራቱ …
በሸክላው
ባራቱ …
ይጠገንለታል
እንደስብራቱ …
ለነገ
ብሥራቱ …
አለ አክሱም
በምፅዓት
ስም …
ምዕራፍ
ሁለት!
እንግዲህ
… ከእጅህ በጉንጭህ …
ኃላ እንዳይቆጭህ
…
ምግባር
እስኪያጭህ …
እንኳንስ
ራብ አሞራ ይንጭህ!
ምንም አስተያየቶች የሉም