Latest

ads header

ዜና

አሜሪካ ከካቡሉ ጥቃት ጋር በተያያዘ የአጸፋ እርምጃ ወሰደች።

አሜሪካ ከካቡሉ ጥቃት ጋር በተያያዘ የአጸፋ እርምጃ ወሰደች።


አሜሪካ በአፍጋኒስታን ካቡል ሃሚድ ካርዛይ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ከተፈጸመው ጥቃት ጋር በተያያዘ የአጸፋ እርምጃ ወሰደች፡፡


በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) የታገዘው የአጸፋ እርምጃ አሜሪካ ጥቃቱን አቀናብሯል ባለችውና ለጥቃቱም ኃላፊነቱን በወሰደው የአይ ኤስ አይኤስ የአፍጋኒስታን ክንፍ (ISIS-Khorasan) ላይ የተወሰደ ነው፡


በምስራቃዊ ናንጋርሃር ክልል በተፈጸመው በዚህ ጥቃት ዒላናዬ ነበር ያለችውን አንድን ሰው ግደሏን አሜሪካ አስታውቃለች፡፡


ጥቃቱ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለካቡሉ ጥቃት የአጸፋ ምላሽን እንደሚሰጡ በዛቱ በማግስቱ የተፈጸመ ነው፡፡


በሃሚድ ካርዛይ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ እና በአቅራቢያው በሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ በተፈጸመው ጥቃት 13 የአሜሪካ ሰራተኞች እና 170 አፍጋናውያን ሞተዋል፡፡


ምንም አስተያየቶች የሉም