Latest

ads header

ዜና

የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ባንክ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር የንግድ ባንኮችን የጥሬ ገንዘብ መጠባበቂያ ጥምርታ በእጥፍ ማሳደጉን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕንፃ


ሮይተርስ ከአዲስ አበባ እንደዘገበው ከመስከረም 1 ቀን 2021 ጀምሮ ባንኮች ከሚሰበሰቡት የተጣራ ቁጠባ በኢትዮጵያ ማዕከላዊ  ባንክ እንዲያስቀ የሚገደዱትን የመጠባበቂያ መጠን 5 በመቶ ወደ 10 በመቶ ከፍ ተደርጓል፡፡ የንግድ ባንኮችም  ለአጭር ጊዜ  ብድር  ለማዕከላዊ ባንክ የሚከፍሉት ወለድ 13%  ወደ 16% ማደጉን የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ባንክ ትናንት ባውጣው በመግለጫ አመልክቷል። 

 

አበዳሪዎችም፤ ከላኪዎች እና ከእርዳታ ድርጅቶች የሚያገኙትን የውጭ  ምንዛሬ ድጋፍ  ወደ ማዕከላዊ ባንክ  እንዲያቀርቡ የሚጠየቁት 30 በመቶ  ወደ  50 በመቶ ከፍ ብሏል።በኢትዮጵያ የዕዝና እና የቁጥጥር ኢኮኖሚ ውስጥ መንግሥት የባንኮችን የውጭ ምንዛሪ ምደባ ይቆጣጠራል ሲልም ዘገባው አክሏል።

 

እንደ ማዕከላዊ ባንክ  ይህ ድንጋጌ የመንግስትን የውጭ  ምንዛሬ የገቢ  በማሳደግ  የውጭ ዕዳን  የመክፈል  አቅም የሚጨመር ነው።ከዚህ በተጨማሪ እርምጃው  የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እና  የመሠረታዊ ሸቀጦችን ወደ ሀገር የማስገባት  አቅምን ያሳድጋል ተብሏል

 

እንደ ሮይተርስ ዘገባ በሀገሪቱ ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር 26.4% የነበረ ሲሆን፤ ዓመቱን ሙሉ ግን  የግሽበት መጠኑ ወደ 20%  የተጠጋ ነበር። ይህም  መንግሥት ችግሩን ለመግታት  የሚያደርገውን  ጥረት  የሚጣረስ ነው ብሏል።

 

የቻይናው ኤግዚም ባንክ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ብድር መስጠት እያደገ የመጣውን የውጭ ዕዳ እና የመክፈል ችግሮች ሊያባብሰው ይችላል በሚል፤ ወደ 339 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ብድር ማገዱን አንድ የኢትዮጵያ የመንግስት ባለሥልጣን በዚህ ወር መናገራቸው ይታወሳል።







ምንም አስተያየቶች የሉም