Latest

ads header

ዜና

ተሰብሮ የነበረው የተከዜ ድልድይ ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

የተከዘ ድልድይ ከግንባታ በኋላ / ምስል፡ የትግራይ መገናኛ ብዙሐን

 በኢትዮጵያ ሰሜናዊ ክፍል በትግራይ ክልል የሚገኘው የተከዜ ድልድይ ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡


ከመቶ ሜትር በላይ ርዝመት ያለው ድልድዩ ሽሬ ከተማን ከማይፀብሪ ጋር የሚያገናኝና አገልግሎት በመስጠት ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረ ነው፡፡

 

ባለፈው ጥቅምት 24 የፌደራሉ መንግሥት የሰሜን ዕዝ በህወሓት ጥቃት እንደደረሰበት ገልፆ ‹‹ሕግን የማስከበር›› ባለው ጦርነት ምክንያት በተካሄደው ውጊያ ምክንያት ነበር ድልድዩ ሊሰበር የቻለው፡፡

 

ምንም እንኳን ድልድዩ በጦርነቱ ምክንያት ቢሰበርም በማን ምክንያት እንደተሰበረ ግን በግልፅ አልታወቀም፡፡

 

የተከዘ ድልድይ በግንባታ ወቅት / ምስል፡ የትግራይ መገናኛ ብዙሐን

በትግራይ ክልል መንግሥት የሚተዳደረው የትግራይ ቴሌቪዥን በምስል አስደግፎ ባወጣው ዘገባ ላይ ድልድዩ እንደገና ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡

 

ሁለት ወራት ገደማ ከአገልግሎት ውጭ በመሆኑ በክልሉ ያሉ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚሹ ዜጎችን ጉዳት የከፋ እንዳደረገው የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ሲገልፁ ቆይተዋል፡፡

የቴሌቪዥን ጣቢያው ድልድዩ በራስ አቅም ተገንብቷል ቢልም የጥራት ሁኔታውንና ምን ያህል ወጪ እንደተደረገበት ግን ያለው ነገር የለም፡፡

 

የተከዘ ድልድይ ከግንባታ በኋላ / ምስል፡ የትግራይ መገናኛ ብዙሐን

በትግራይ ክልል የተጀመረው ጦርነት የውጭ ሃገራት በቀጥታና በተዘዋዋሪ ተሳትፈውበት በርካቶችን ለህልፈተ ሕይወትና ለጉዳት አጋልጦ ወደ አማራና ዓፋር ክልሎች ተስፋፍቷል፡፡


ተሰበረው የተከዘ ድልድይ / ምስል፡ AP


 

ምንም አስተያየቶች የሉም