Latest

ads header

ዜና

ዶ/ር ይልቃል ከፋለ የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ሆነው ተሸሙ



የክልሉ ምከር ቤት አዲስ አፈ ጉባዔ እና ምክትል አፈ ጉባዔም ሰይሟል። 


የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት መስረታ በዛሬው እለት እየተካሄደ ይገኛል። 


ምክር ቤቱ ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋዬ አለሙ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ፣ አቶ አማረ ሰጤ ምክትል አፈ ጉባዔ አድርጎ ሾሟል። 


በተጨማሪም የአማራ ክልል ምክር ቤት ዶ/ር ይልቃል ከፋለን የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አድርጎ ሾሟል። 


ዶ/ር ይልቃል ከፋለ በተለያዩ ትምህርት ኮሌጆች በመምህርነት፣ ዲን በመሆንና በደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና ፕሬዝዳንት በመሆን ውጤታማ ኃላፊነትን የተወጡ አመራር መሆናቸው ተገልጿል።

ምንም አስተያየቶች የሉም