Latest

ads header

ዜና

አየርላንድ የጸጥታው ምክር ቤት የመስከረም ወር ሰብሳቢነትን ከህንድ ተረከበች

የጸጥታው ምክር ቤት


የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የወርሃ መስከረም ሰብሳቢ አየርላንድ ሆና ተመረጠች፡፡

ተ.መ.ድ. በትግራይ ክልል ጉዳይ ስምንት ጊዜ እንዲወያዩ ካደረጉ ሃገራት መካከል አንዷ የሆነቺው አየርላንድ ሰብሳቢነቱን ከህንድ ነው የተረከበችው፡፡

የወርሃ ነሃሴ የምክር ቤቱ ሰብሳቢ የነበረችው ህንድ ምክር ቤቱ በትግራይ ጉዳይ በተወያየበት ጊዜ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ‹‹ጣልቃ መገባት የለበትም›› ስትል በመቃወም ከኢትዮጵያ መንግስት ጎን መቆሟ የሚታወስ ነው፡፡

ወቅታዊ የኢትዮጵያን ሁኔታዎች በአሳሳቢነት ስትገልጽ የሰነበተችው አየርላንድ በበኩሏ ከአሁን ቀደም ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ አስቸኳይ ስብሰባን እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረቧ የሚታወስ ነው፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም